ሩት Chapter 3

For English

Read ሩት Chapter 3 Online

Read ሩት Chapter 3 online from the Holy Bible. This chapter is part of the Book of ሩት in the Old Testament. Browse every verse with easy chapter navigation, continue to the next chapter, or explore the complete Book of ሩት and the Holy Bible online.

Choose a Chapter

ሩት 3

ምዕራፍ 3

1. አማትዋም ኑኃሚን አለቻት። ልጄ ሆይ፥ መልካም እንዲሆንልሽ ዕረፍት አልፈልግልሽምን?

2. ፤ አሁንም ከገረዶቹ ጋር የነበርሽበት ቦዔዝ ዘመዳችን አይደለምን? እነሆ፥ እርሱ በዛሬ ሌሊት በአውድማው ላይ ገብሱን በመንሽ ይበትናል።

3. ፤ እንግዲህ ታጠቢ፥ ተቀቢ፥ ልብስሽን ተላበሺ፥ ወደ አውድማውም ውረጂ፤ ነገር ግን መብሉንና መጠጡን እስኪጨርስ ድረስ ለሰውዮው አትታዪው።

4. ፤ በተኛም ጊዜ የሚተኛበትን ስፍራ ተመልከቺ፥ ገብተሽም እግሩን ግለጪ፥ ተጋደሚም፤ የምታደርጊውንም እርሱ ይነግርሻል።

5. ፤ ሩትም። የተናገርሽኝን ሁሉ አደርጋለሁ አለቻት።

6. ፤ ወደ አውድማውም ወረደች፥ አማትዋም ያዘዘቻትን ሁሉ አደረገች።

7. ፤ ቦዔዝም ከበላና ከጠጣ ሰውነቱንም ደስ ካሰኘ በኋላ፥ በእህሉ ክምር አጠገብ ሊተኛ ሄደ፤ ሩትም በቀስታ መጣች፥ እግሩንም ገልጣ ተኛች።

8. ፤ መንፈቀ ሌሊትም በሆነ ጊዜ ሰውዮው ደነገጠ፥ ዘወርም አለ፤ እነሆም፥ አንዲት ሴት በእግርጌው ተኝታ ነበረች።

9. ፤ እርሱም። ማን ነሽ? አለ። እርስዋም። እኔ ባሪያህ ሩት ነኝ፤ ዋርሳዬ ነህና ልብስህን በባሪያህ ላይ ዘርጋ አለችው።

10. ፤ ቦዔዝም አላት። ልጄ ሆይ፥ በእግዚአብሔር የተባረክሽ ሁኚ፤ ባለጠጋም ድሀም ብለሽ ጐበዛዝትን አልተከተልሽምና ከፊተኛው ይልቅ በመጨረሻው ጊዜ ቸርነት አድርገሻል።

11. ፤ አሁንም፥ ልጄ ሆይ፥ አትፍሪ፤ በአገሬ ያሉ ሕዝብ ሁሉ ምግባረ መልካም ሴት እንደ ሆንሽ ያውቃሉና ያልሽውን ነገር ሁሉ አደርግልሻለሁ።

12. ፤ የቅርብ ዘመድ መሆኔ እውነት ነው፤ ነገር ግን ከእኔ የቀረበ ዘመድ አለ።

13. ፤ ዛሬ ሌሊት እደሪ፤ ነገም እርሱ ዋርሳ መሆን ቢወድድ መልካም ነው፥ ዋርሳ ይሁን፤ ዋርሳ ሊሆን ባይወድድ ግን፥ ሕያው እግዚአብሔርን እኔ ዋርሳ እሆንሻለሁ፤ እስኪነጋ ድረስ ተኚ።

14. ፤ እስኪነጋም በእግርጌው ተኛች፤ ቦዔዝም። ሴት ወደ አውድማው እንደ መጣች ማንም እንዳያውቅ ብሎ ነበርና ገና ሰውና ሰው ሳይተያይ ተነሣች።

15. ፤ እርሱም። የለበስሽውን ኩታ አምጥተሽ ያዢው አላት፤ በያዘችም ጊዜ ስድስት መስፈሪያ ገብስ ሰፈረላት አሸከማትም።

16. ፤ እርሱም ወደ ከተማይቱ ሄደ። ወደ አማትዋም መጣች፥ አማትዋም። ልጄ ሆይ እንዴት ነሽ? አለቻት፤ እርስዋም ሰውዮው ያደረገላትን ሁሉ ነገረቻት።

17. ፤ ወደ አማትሽ ባዶ እጅሽን አትሂጂ ብሎ ይህን ስድስት መስፈሪያ ገብስ ሰጠኝ አለቻት።

18. ፤ እርስዋም። ልጄ ሆይ፥ ሰውዮው ይህን ነገር ዛሬ እስኪጨርስ ድረስ አያርፍምና ፍጻሜው እስኪታወቅ ድረስ ዝም በዪ አለች።

About ሩት Chapter 3

Read ሩት Chapter 3 online from the Holy Bible. This chapter is part of the Book of ሩት in the Old Testament. Continue reading with the chapter navigation above or explore the complete book.

Book Information

Book: ሩት
Chapter: 3
Testament: Old Testament

How to Read this Chapter

Use the Previous and Next Chapter buttons to continue reading ሩት. You can also adjust the font size for comfortable reading and browse other books of the Bible using the navigation links.

https://www.youtube.com/watch?v=rzsT_Q3KLzE

More Resources

Continue Reading the Bible

Continue reading ሩት Chapter 3 and explore every book, chapter and verse of the Holy Bible. Use the navigation links above and below to move through the Scriptures with ease.

Frequently Asked Questions

What is ሩት Chapter 3?

ሩት Chapter 3 is part of the Book of ሩት in the Holy Bible.

Can I read this chapter online?

Yes. You can read the complete ሩት Chapter 3 online for free with easy chapter navigation.

More Chapters from ሩት

  1. ሩት Chapter 1
  2. ሩት Chapter 4
  3. ሩት Chapter 2

Explore More from ብሉይ ኪዳን

  1. መሳፍንት Chapter 1
  2. አስቴር Chapter 7
  3. ኢዮብ Chapter 41
  4. ሕዝቅኤል Chapter 11
  5. ዘጸአት Chapter 38
  6. ኢዮብ Chapter 28
  7. ዘፍጥረት Chapter 2

Related Chapters & Readings

  1. ዘዳግም Chapter 32
  2. ኤርምያስ Chapter 24
  3. መዝሙረ ዳዊት Chapter 140
  4. ኤርምያስ Chapter 46
  5. 2 ዜና መዋዕል Chapter 4
  6. 2 ቆሮንቶስ Chapter 7
  7. ማቴዎስ Chapter 11
Share Your Love

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *